ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 13:9-16 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

9. እነሆ፤ የእግዚአብሔር ቀን ጨካኝ ነው፤ምድርን ባድማ ሊያደርጋት፣በውስጧም ያሉትን ኀጢአተኞች ሊያጠፋ፣ከመዓትና ከብርቱ ቍጣ ጋር ይመጣል።

10. የሰማይ ከዋክብትና ሰራዊታቸው፣ብርሃን አይሰጡም፤ፀሓይ ገና ከመውጣቷ ትጨልማለች፤ጨረቃም ብርሃኗን አትሰጥም።

11. ዓለምን ስለ ክፋቷ፣ክፉዎችንም ስለ ኀጢአታቸው እቀጣለሁ፤የትዕቢተኞችን እብሪት እሽራለሁ፤የጨካኞችንም ጒራ አዋርዳለሁ።

12. ሰውን ከነጠረ ወርቅ ይልቅ ውድ፣ከኦፊርም ወርቅ ይበልጥ ብርቅ አደርጋለሁ።

13. ስለዚህ በሰራዊት ጌታ በእግዚአብሔር መዓት፣ቍጣው በሚነድበት ቀን፣ሰማያትን እነቀንቃለሁ፤ምድርንም ከስፍራዋ አናውጣለሁ።

14. እንደሚታደን ሚዳቋ፣እረኛም እንደሌለው የበግ መንጋ፣እያንዳንዱ ወደ ወገኑ ይመለሳል፣እያንዳንዱም ወደ አገሩ ይሸሻል።

15. የተማረከ ሁሉ ይወጋል፤የተያዘም ሁሉ በሰይፍ ይወድቃል።

16. ዐይናቸው እያየ ሕፃናታቸው ይጨፈጨፋሉ፤ቤታቸው ይዘረፋል፤ ሚስቶቻቸው ይደፈራሉ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 13