1. ጌታ እግዚአብሔር ስለ ኤዶም እንዲህ ይላል፤ ከእግዚአብሔር ዘንድ መልእክት ሰምተናል፤መልእክተኛውም ወደ አሕዛብ ተልኮ እንዲህብሎአል፤“ተነሡ፤ እርሷን ለመውጋት እንውጣ።”
2. “እነሆ፤ በአሕዛብ መካከል ታናሽ አደርግሃለሁ፤እጅግ የተናቅህ ትሆናለህ።
3. አንተ በሰንጣቃ ዐለት ውስጥየምትኖር፣መኖሪያህንም በከፍታ ስፍራ ያደረግህ፣ለራስህም፣“ማን ወደ ምድር ሊያወርደኝ ይችላል?” የምትል፣የልብህ ትዕቢት አታልሎሃል።