ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

አሞጽ 8:3-7 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

3. ጌታ እግዚአብሔር፣ “በዚያ ቀን የቤተ መቅደሱ ዝማሬ ወደ ዋይታ ይለወጣል፤ እጅግ ብዙ የሆነ የሰው ሬሳ ወድቆ ይገኛል፤ ዝምታም ይሰፍናል” ይላል።

4. እናንት ችግረኞችን የምትረግጡ፣የምድሪቱንም ድኾች የምታጠፉ ይህን ስሙ፤

5. እንዲህም ትላላችሁ፤“መስፈሪያውን በማሳነስ፣ዋጋውን ከፍ በማድረግ፣በሐሰተኛ ሚዛን በማጭበርበር፣እህል እንድንሸጥ፣የወር መባቻ መቼ ያበቃል?ስንዴም ለገበያ እንድናቀርብ፣ሰንበት መቼ ያልፋል?”

6. ድኻውን በብር፣ችግረኛውንም በጥንድ ጫማ እንገዛለን፤ግርዱን እንኳ በስንዴ ዋጋ እንሸጣለን።”

7. እግዚአብሔር በያዕቆብ ክብር እንዲህ ሲል ምሎአል፤ “እነርሱ ያደረጉትን ሁሉ ከቶ አልረሳም።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ አሞጽ 8