ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

አሞጽ 6 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

ተዘልላ ላለችው እስራኤል የተሰጠ ማስጠንቀቂያ

1. በጽዮን ተዘልላችሁ የምትቀመጡ፣በሰማርያ ተራራ ያለ ሥጋት የምትኖሩ፣የእስራኤልም ሕዝብ ለርዳታ ወደ እናንተ የሚመጡባችሁ፣እናንት የአሕዛብ አለቆች ሆይ፤ ወዮላችሁ!

2. ወደ ካልኔ ሂዱ፤ እርሱንም ተመልከቱ፤ከዚያም ወደ ታላቂቱ ሐማት ሂዱ፤ወደ ፍልስጥኤም ከተማ ወደ ጌትም ውረዱ፤እነዚህ ከሁለቱ መንግሥታቶቻችሁ ይሻላሉን?የምድራቸውስ ስፋት ከእናንተ ይበልጣልን?

3. ክፉውን ቀን ለምታርቁ፣የግፍንም ወንበር ለምታቀርቡ ወዮላችሁ!

4. በዝሆን ጥርስ ባጌጠ ዐልጋ ላይ ለምትተኙ፤በድንክ ዐልጋችሁ ላይ ለምትዝናኑ፣ከበጎች መንጋ ጠቦትን፣ከጋጣም ጥጃን ለምትበሉ፤

5. ባልተቃኘ በገና ለምትዘፍኑ፣በሙዚቃ መሣሪያ ለመጫወት ለምትሹ፣

6. በፋጋ የወይን ጠጅ ለምትጠጡ፣ምርጥ ሽቱም ለምትቀቡ፣ስለ ዮሴፍ መከራ ግን ለማታዝኑ ወዮላችሁ!

7. ስለዚህ እናንተ በመጀመሪያ በምርኮ ከሚወሰዱት መካከል ናቸሁ፤መፈንጠዛችሁና መዝናናታችሁም ያበቃል።

እግዚአብሔር የእስራኤልን ትዕቢት ይጸየፋል

8. ጌታእግዚአብሔር “የያዕቆብን ትዕቢት ተጸይፌአለሁ፤ምሽጎቹንም ጠልቻለሁ፤ከተማዪቱንና በውስጥዋ ያለውን ሁሉ፣አሳልፌ እሰጣለሁ” ሲል በራሱ ምሎአል፤ይላል የሰራዊት አምላክ እግዚአብሔር።

9. በአንድ ቤት ውስጥ ዐሥር ሰዎች ቢቀሩ እነርሱም ይሞታሉ።

10. በድኖቹንም ከቤት አውጥቶ ማቃጠል ያለበት አንድ ዘመድ መጥቶ ተደብቆ ያለውን ሰው፣ “ከአንተ ጋር የቀረ ሌላ ሰው አለን?” ሲለው፣ እርሱም “የለም” ይለዋል፤ ከዚያም በኋላ፣ “ዝም በል፤ የእግዚአብሔርን ስም መጥራት አይገባንም” ይለዋል።

11. እነሆ፤ እግዚአብሔር ትእዛዝ ሰጥቶአልና፤ታላላቅ ቤቶችን ያወድማቸዋል፤ትንንሾቹንም ያደቅቃቸዋል።

12. ፈረሶች በጭንጫ ላይ ይሮጣሉን?ሰውስ እዚያ ላይ በበሬ ያርሳልን?እናንተ ግን ፍትሕን ወደ መርዝነት፣የጽድቅንም ፍሬ ወደ መራራነት ለወጣችሁ።

13. እናንተ ሎዶባርን በማሸነፋችሁ ደስ ያላችሁ፣“ቃርናይምን በራሳችን ብርታት ይዘናል” የምትሉ፣

14. ሁሉን የሚገዛ አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፣“የእስራኤል ሕዝብ ሆይ፤ እነሆ፤ እኔ ከሐማት መግቢያ እስከ ዓረባ ሸለቆ ድረስ፣የሚያስጨንቃችሁን ሕዝብ፣ በእናንተላይ አስነሣለሁ።”