ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

አሞጽ 3:11-15 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

11. ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ጠላት ምድሪቱን ይወራል፤ምሽጎቻችሁን ያፈርሳል፤ ድንኳኖቻችሁንይዘርፋል።”

12. እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“እረኛ ከአንበሳ መንጋጋ፣ሁለት የእግር ዐጥንት ወይም የጆሮ ቍራጭ እንደሚያድን፣እንዲሁም በሰማርያ በዐልጋቸው ጫፍ ላይ፣በደማስቆም በምንጣፋቸው ላይ የተቀመጡ፣እስራኤላውያን ይድናሉ።”

13. “ይህን ስሙ፤ በያዕቆብም ቤት ላይ መስክሩ” ይላል ጌታ፣ ሁሉን የሚገዛ አምላክ እግዚአብሔር።

14. “እስራኤልን ስለ ኀጢአቷ በምቀጣበት ቀን፣የቤቴልን መሠዊያዎች አፈርሳለሁ፤የመሠዊያው ቀንዶች ይቈረጣሉ፤ወደ ምድርም ይወድቃሉ።

15. የክረምቱን ቤት፣ከበጋው ቤት ጋር እመታለሁ፤በዝሆን ጥርስ ያጌጡ ቤቶችም ይደመሰሳሉ፤ታላላቅ አዳራሾችም ይፈርሳሉ፤”ይላልእግዚአብሔር።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ አሞጽ 3