ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

አሞጽ 1:8-11 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

8. በአስቀሎና በትር የያዘውን፣የአሸዶድንም ንጉሥ እደመስሳለሁ፤ በፍልስጥኤም ካሉት የመጨረሻው ሰውእስኪሞት ድረስ፣እጄን በአቃሮን ላይ እዘረጋለሁ፤”ይላል ጌታ እግዚአብሔር።

9. እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ስለ ሦስቱ የጢሮስ ኀጢአት፣ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቊጣዬን አልመልስም።የወንድማማችነትን ቃል ኪዳን በማፍረስ፣ሕዝቡን ሁሉ ማርካ ለኤዶም ሸጣለችና።

10. ምሽጎችዋን እንዲበላ፣በጢሮስ ቅጥሮች ላይ እሳት እሰዳለሁ።”

11. እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ስለ ሦስቱ የኤዶም ኀጢአት፣ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቊጣዬን አልመልስም፤ርኅራኄን በመንፈግ፣ወንድሙን በሰይፍ አሳዶታልና፤የቊጣውንም ነበልባል ሳይገድብ፣መዓቱን ሳያቋርጥ አውርዶበታልና፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ አሞጽ 1