ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ናሆም 2:10-13 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

10. ተበዝብዛለች፤ ተዘርፋለች፤ ተራቍታለች።ልብ ቀልጦአል፤ ጒልበት ተብረክርኮአል፤ሰውነት ተንቀጥቅጦአል፤ ፊት ሁሉ ገርጥቶአል።

11. አሁን ታዲያ የአንበሶቹ ዋሻ፣ደቦሎቻቸውን ያበሉበትወንዱና ሴቷ አንበሳ የሄዱበት፣ግልገሎችም ሳይፈሩ የተሰማሩበት ቦታ ወዴት ነው?

12. አንበሳው ለግልገሎቹ የሚበቃውን ያህል ገደለ፤ለእንስቶቹም ዐንቆ ገደለላቸው፤የገደለውን በማረፊያ ቦታው፣የነጠቀውንም በዋሻው ሞልቶታል።

13. የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“በእናንተ ላይ ተነሥቼባችኋለሁ፤ሠረገሎቻችሁን አቃጥዬ አጨሳለሁ፤ደቦል አንበሶቻችሁን ሰይፍ ይበላል፤የምትበሉትን በምድር ላይ አልተውላችሁም፤የመልእክተኞቻችሁም ድምፅ፣ከእንግዲህ ወዲያ አይሰማም።”

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ናሆም 2