ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ናሆም 1:7-12 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

7. እግዚአብሔር መልካም ነው፤በጭንቅ ጊዜም መሸሸጊያ ነው።ለሚታመኑበት ይጠነቀቅላቸዋል፤

8. ነነዌን ግን፣በሚያጥለቀልቅ ጐርፍ ያጠፋታል፤ጠላቶቹንም ወደ ጨለማ ያሳድዳቸዋል።

9. በእግዚአብሔር ላይ ምንም ቢያሤሩ፣እርሱ ያጠፋዋል፤መከራም ዳግመኛ አይነሣም።

10. በእሾህ ይጠላለፋሉ፤በወይን ጠጃቸውም ይሰክራሉ፤እሳትም እንደ ገለባ ይበላቸዋል።

11. ነነዌ ሆይ፤ በእግዚአብሔር ላይ የሚያሤር፣ክፋትንም የሚመክር፣ከአንቺ ዘንድ ወጥቶአል።

12. እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ምንም ኀይለኞችና ብዙዎች ቢሆኑም፣ይቈረጣሉ፤ ይጠፋሉም።ይሁዳ ሆይ፤ ከዚህ በፊት ባስጨንቅህም፣ከእንግዲህ አላስጨንቅህም።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ናሆም 1