ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ናሆም 1:3-9 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

3. እግዚአብሔር ለቍጣ የዘገየ በኀይሉም ታላቅ ነው፤ እግዚአብሔር በደለኛውን ሳይቀጣ አያልፍም፤መንገዱ በዐውሎ ነፋስና በማዕበል ውስጥ ነው፤ደመናም የእግሩ ትቢያ ነው።

4. ባሕርን ይገሥጻል፤ ያደርቀዋልም፤ወንዞችን ሁሉ ያደርቃል።ባሳንና ቀርሜሎስ ጠውልገዋል፤የሊባኖስም አበቦች ረግፈዋል።

5. ተራሮች በፊቱ ታወኩ፤ኰረብቶችም ቀለጡ።ምድር በፊቱ፣ዓለምና በውስጧ የሚኖሩት ሁሉ ተናወጡ።

6. ቊጣውን ማን ሊቋቋም ይችላል?ጽኑ ቊጣውንስ ማን ሊሸከም ይችላል?መዓቱ እንደ እሳት ፈሶአል፤ዐለቶችም በፊቱ ተሰነጣጥቀዋል።

7. እግዚአብሔር መልካም ነው፤በጭንቅ ጊዜም መሸሸጊያ ነው።ለሚታመኑበት ይጠነቀቅላቸዋል፤

8. ነነዌን ግን፣በሚያጥለቀልቅ ጐርፍ ያጠፋታል፤ጠላቶቹንም ወደ ጨለማ ያሳድዳቸዋል።

9. በእግዚአብሔር ላይ ምንም ቢያሤሩ፣እርሱ ያጠፋዋል፤መከራም ዳግመኛ አይነሣም።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ናሆም 1