ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ናሆም 1:1-6 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. ስለ ነነዌ ጥፋት የተነገረ ንግር፤ የኤልቆሻዊው የናሆም የራእዩ መጽሐፍ ይህ ነው፤

2. እግዚአብሔር ቀናተኛና ተበቃይ አምላክ ነው፤ እግዚአብሔር የሚበቀል፣ በመዓትም የተሞላ ነው። እግዚአብሔር ባላጋራዎቹን ይበቀላል፤በጠላቶቹም ላይ ቍጣውን ያመጣል

3. እግዚአብሔር ለቍጣ የዘገየ በኀይሉም ታላቅ ነው፤ እግዚአብሔር በደለኛውን ሳይቀጣ አያልፍም፤መንገዱ በዐውሎ ነፋስና በማዕበል ውስጥ ነው፤ደመናም የእግሩ ትቢያ ነው።

4. ባሕርን ይገሥጻል፤ ያደርቀዋልም፤ወንዞችን ሁሉ ያደርቃል።ባሳንና ቀርሜሎስ ጠውልገዋል፤የሊባኖስም አበቦች ረግፈዋል።

5. ተራሮች በፊቱ ታወኩ፤ኰረብቶችም ቀለጡ።ምድር በፊቱ፣ዓለምና በውስጧ የሚኖሩት ሁሉ ተናወጡ።

6. ቊጣውን ማን ሊቋቋም ይችላል?ጽኑ ቊጣውንስ ማን ሊሸከም ይችላል?መዓቱ እንደ እሳት ፈሶአል፤ዐለቶችም በፊቱ ተሰነጣጥቀዋል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ናሆም 1