ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሰቆቃወ 4:17-21 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

17. ከሁሉም በላይ በከንቱ ርዳታን ስንጠባበቅ፣ዐይኖቻችን ደከሙ፤ከግንብ ማማችን ላይ ሆነን፣ሊያድን ከማይችል ሕዝብ ርዳታ ጠበቅን።

18. ሰዎች እግር እግራችንን ተከታተሉን፤ስለዚህ በመንገዳችን መሄድ አልቻልንም፤መጨረሻችን ቀርቦአል፤ ቀኖቻችንም ተቈጥረዋል፤ፍጻሜያችን መጥቶአልና።

19. ከሰማይ ንስሮች ይልቅ፣ጠላቶቻችን ፈጣኖች ናቸው፤በተራሮች ላይ አሳደዱን፤በምድረ በዳም ሸመቁብን።

20. በእግዚአብሔር የተቀባው፣ የሕይወታችን እስትንፋስ፣በወጥመዳቸው ተያዘ፤በጥላው ሥር፣በአሕዛብ መካከል እንኖራለን ብለን አስበን ነበር።

21. አንቺ በዖፅ ምድር የምትኖሪ፣የኤዶምያስ ሴት ልጅ ሆይ፤ ደስ ይበልሽ፤ ሐሴትም አድርጊነገር ግን ለአንቺም ደግሞ ጽዋው ይደርስሻል፤ትሰክሪያለሽ፤ ዕርቃንሽንም ትጋለጫለሽ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሰቆቃወ 4