ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሰቆቃወ 3:6-16 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

6. ከሞቱ ብዙ ጊዜ እንደሆናቸው፣በጨለማ እንድኖር አደረገኝ።

7. በቅጥር ውስጥ ዘጋብኝ፤ ስለዚህ ማምለጥ አልቻልሁም፤የእስር ሰንሰለቴንም አከበደብኝ።

8. ርዳታ ፈልጌ ብጣራና ብጮኽ እንኳ፣ጸሎቴን መስማት አልፈለገም።

9. መንገዴን በተጠረቡ ድንጋዮች ዘጋ፤ጐዳናዬንም አጣመመ።

10. አሸምቆ እንደ ተኛ ድብ፣እንደ አደባም አንበሳ፣

11. ከመንገድ ጐትቶ አስወጣኝ፤ ቈራረጠኝም፤ያለ ረዳትም ተወኝ።

12. ቀስቱን ገተረ፤ለፍላጻዎቹም ዒላማ አደረገኝ።

13. ፍላጻዎችን ከሰገባው አውጥቶ፣ልቤን ወጋው።

14. ለሕዝቤ ሁሉ ማላገጫ ሆንሁኝ፤ቀኑን ሙሉ በመሣለቅ ያዜሙብኛል።

15. መራራ ሥር አበላኝ፤ሐሞትም አጠገበኝ።

16. ጥርሴን በድንጋይ ሰበረ፤በትቢያ ውስጥ ረጋገጠኝ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሰቆቃወ 3