ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሰቆቃወ 3:37-51 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

37. እግዚአብሔር ካላዘዘ በቀር፤ተናግሮ መፈጸም የሚችል ማን ነው?

38. ክፉም ሆነ መልካም ነገር፣ከልዑል አፍ የሚወጣ አይደለምን?

39. ታዲያ ሕያው ሰው በኀጢአቱ ሲቀጣ፣ስለ ምን ያጒረመርማል?

40. መንገዳችንን እንመርምር፤ እንፈትን፤ወደ እግዚአብሔርም እንመለስ።

41. ልባችንን ከእጃችን ጋር በሰማይ ወዳለው ወደ አምላካችንእናንሣ፤ እንዲህም እንበል፤

42. “ዐምፀናል፤ ኀጢአትም ሠርተናል፤አንተም ይቅር አላልኸንም።

43. “ራስህን በቊጣ ከደንህ፤ አሳደድኸንም፤ያለ ርኅራኄም ገደልኸን።

44. ጸሎት እንዳያልፍ፣ራስህን በደመና ሸፈንህ።

45. በአሕዛብ መካከል፣አተላና ጥራጊ አደረግኸን።

46. “ጠላቶቻችን ሁሉ፣አፋቸውን በእኛ ላይ ከፈቱ።

47. በጥፋትና በመፈራረስ፣በችግርና በሽብር ተሠቃየን።

48. የእንባ ጐርፍ ከዐይኔ ፈሰሰ፤ሕዝቤ አልቋልና።

49. ያለ ዕረፍት፣ያለ ማቋረጥ ዐይኖቼ እንባ ያፈሳሉ፤

50. እግዚአብሔር ከላይ፣ከሰማይ እስኪያይ ድረስ።

51. በከተማዬ ባሉት ሴቶች ሁሉ ላይ የደረሰውን ማየቴ፣ነፍሴን አስጨነቃት።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሰቆቃወ 3