ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሰቆቃወ 2 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. እግዚአብሔር የጽዮንን ሴት ልጅ፣በቍጣው ደመና እንዴት ጋረዳት!ከሰማይ ወደ ምድር፣የእስራኤልን ክብር ወርውሮ ጣለው፤በቍጣው ቀን፣የእግሩን መቀመጫ አላስታወሰም።

2. የያዕቆብን መኖሪያ ሁሉ፣እግዚአብሔር ያለ ርኅራኄ ዋጣቸው፤የይሁዳን ሴት ልጅ ምሽጎች፣በቍጣው አፈረሳቸው፤መንግሥቷንና መሳፍንቷን፣በማዋረድ ወደ ምድር ጣላቸው።

3. በጽኑ ቍጣው፣የእስራኤልን ቀንድ ሁሉ ሰበረ፤ጠላት በተቃረበ ጊዜ፣ቀኝ እጁን ወደ ኋላ መለሰ፤በዙሪያው ያለውን ሁሉ እንደሚበላ እሳት፣በያዕቆብ ላይ የእሳት ነበልባል ነደደ።

4. እንደ ጠላት ቀስቱን ገተረ፤ቀኝ እጁ ተዘጋጅታለች፤ለዐይን ደስ የሚያሰኙትን ሁሉ፤እንደ ጠላት ዐረዳቸው፤በጽዮን ሴት ልጅ ድንኳን ላይ፣ቍጣውን እንደ እሳት አፈሰሰ።

5. እግዚአብሔር እንደ ጠላት ሆነ፤እስራኤልንም ዋጠ፤ቤተ መንግሥቶቿን ሁሉ ዋጠ፤ምሽጎቿን አፈራረሰ፤በይሁዳ ሴት ልጅ፣ለቅሶንና ሰቈቃን አበዛ።

6. ማደሪያውን እንደ አትክልት ስፍራ ባዶ አደረገ፤መሰብሰቢያ ስፍራውን አፈረሰ፤ እግዚአብሔር ጽዮንን፣ዓመት በዓላቶቿንና ሰንበታቷን እንድትረሳ አደረጋት፤በጽኑ ቍጣው፣ንጉሡንና ካህኑን እጅግ ናቀ።

7. እግዚአብሔር መሠዊያውን ናቀ፤መቅደሱንም ተወ፤የቤተ መንግሥቶቿን ቅጥሮች፣ለጠላት አሳልፎ ሰጠ፤በዓመት በዓል ቀን እንደሚደረገው በእግዚአብሔር ቤት በኀይል ጮኹ።

8. በጽዮን ሴት ልጅ ዙሪያ ያለውን ቅጥር፣ እግዚአብሔር ለማፍረስ ወሰነ፤የመለኪያ ገመድ ዘረጋ፤ከማጥፋትም እጆቹን አልሰበሰበም፤ምሽጎችና ቅጥሮች እንዲያለቅሱ አደረገ፤በአንድነትም ጠፉ።

9. በሮቿ ወደ ምድር ሰመጡ፤የብረት መወርወሪያዎቻቸውን ሰባበረ፤ አጠፋቸውም፤ንጉሥዋና መሳፍንቶቿ በአሕዛብ መካከል ተማርከው ተሰደዋል፤ሕጉ ከእንግዲህ አይኖርም፤ነቢያቶቿም ከእንግዲህ፣ ከእግዚአብሔር ራእይ አያገኙም።

10. የጽዮን ሴት ልጅ ሽማግሌዎች፣በምድር ላይ በዝምታ ተቀምጠዋል፤በራሳቸው ላይ ትቢያ ነሰነሱ፤ማቅም ለበሱ፤የኢየሩሳሌም ወጣት ሴቶች፣ራሳቸውን ወደ ምድር ዝቅ አደረጉ።

11. ዐይኔ በለቅሶ ደከመ፤ነፍሴ በውስጤ ተሠቃየች፤ልቤም በሐዘን ፈሰሰች፣በከተማዪቱ መንገዶች ላይ፣ሕዝቤ ተደምስሰዋልና፤ልጆችና ሕፃናት ደክመዋልና።

12. በከተማዪቱ መንገዶች ላይ፣እንደ ቈሰሉ ሰዎች ሲደክሙ፣በእናታቸው ክንድ ላይ፣ነፍሳቸው በመውጣት ላይ ሳለች፣“እንጀራና የወይን ጠጅ የት አለ?”እያሉ እናቶቻቸውን ይጠይቃሉ።

13. የኢየሩሳሌም ሴት ልጅ ሆይ፤ ስላንቺ ምን ማለት እችላለሁ?ከምንስ ጋር አወዳድርሻለሁ? ድንግሊቱ የጽዮን ልጅ ሆይ፤አጽናናሽ ዘንድ፣በምን ልመስልሽ እችላለሁ?ቍስልሽ እንደ ባሕር ጥልቅ ነው፤ማንስ ሊፈውስሽ ይችላል?

14. የነቢያቶችሽ ራእይ፣ሐሰትና ከንቱ ነው፤ምርኮኛነትሽን ለማስቀረት፣ኀጢአትሽን አይገልጡም።የሚሰጡሽም የትንቢት ቃል፣የሚያሳስትና ከመንገድ የሚያወጣ ነው።

15. በአጠገብሽ የሚያልፉ ሁሉ፣እጃቸውን ያጨበጭቡብሻል፤“የውበት መደምደሚያ፣ የምድር ሁሉ ደስታ፣የተባለች ከተማ ይህች ናትን?”እያሉ ራሳቸውን በመነቅነቅ፣በኢየሩሳሌም ሴት ልጅ ላይ ያሾፋሉ።

16. ጠላቶችሽ ሁሉ በአንድ ላይ፣አፋቸውን በኀይል ከፈቱ፤ጥርሳቸውን እያፏጩ አሾፉ፤እንዲህም አሉ፤ “ውጠናታል፤የናፈቅነው ጊዜ ይህ ነበር፤ኖረንም ልናየው በቃን።”

17. እግዚአብሔር ያሰበውን አደረገ፤ከረዥም ጊዜ በፊት የተናገረውን፣ቃሉን ፈጸመ፤ያለ ርኅራኄ አፈረሰሽ፤ጠላት በሥቃይሽ ላይ እንዲደሰት፣የጠላትሽንም ቀንድ ከፍ ከፍ አደረገ።

18. የሕዝቡ ልብ፣ ወደ እግዚአብሔር ጮኸ።የጽዮን ሴት ልጅ ቅጥር ሆይ፤ቀንና ሌሊት፣እንባሽ እንደ ወንዝ ይፍሰስ፤ለራስሽ ዕረፍትን አትስጪ፣ዐይኖችሽ ከማንባት አያቋርጡ።

19. የሌሊቱ ሰዓት ሲጀምር፣ተነሺ በሌሊት ጩኺ፤በእግዚአብሔር ፊት፣ልብሽን እንደ ውሃ አፍስሺ፤በየመንገዱ ዳር ላይ፣ በራብ ስለወደቁት፣ስለ ልጆችሽ ሕይወት፣ እጆችሽን ወደ እርሱ አንሺ።

20. አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ እይ፤ ተመልከትም፤በማን ላይ እንዲህ አድርገህ ታውቃለህ?በውኑ እናቶች ሕፃኖቻቸውን፣ተንከባክበው ያሳደጓቸውን ልጆች ይብሉን?ካህኑና ነቢዩስ፣በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ውስጥ ይገደሉን?

21. በየመንገዱ ዐቧራ ላይ፣ወጣትና ሽማግሌ በአንድነት ወደቁ፤ወይዛዝርቴና ጐበዛዝቴ፣በሰይፍ ተገደሉ፤በቍጣህ ቀን ገደልሃቸው፤ያለ ርኅራኄም ዐረድሃቸው።