ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 8:3-11 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

3. ወደ ከተማዪቱ በሚያስገቡት በሮች አጠገብ፣በመግቢያዎቹ ላይ፣ ድምጿን ከፍ አድርጋ እንዲህ ስትል ትጮኻለች፤

4. “ሰዎች ሆይ፤ የምጠራውኮ እናንተን ነው፤ለሰው ልጆች ሁሉ ድምፄን ከፍ አደርጋለሁ።

5. እናንተ ብስለት የጐደላችሁ፤ ጠንቃቃነትን ገንዘብ አድርጉ፤እናንተ ተላሎች፤ ማስተዋልን አትርፉ።

6. የምናገረው ጠቃሚ ነገር ስላለኝ አድምጡኝ፤ቀና ነገር ለመናገር ከንፈሮቼን እከፍታለሁ።

7. አንደበቴ እውነትን ይናገራል፤ከንፈሮቼ ክፋትን ይጸየፋሉና።

8. ከአንደበቴ የሚወጡት ቃሎች ሁሉ ጽድቅ ናቸው፤አንዳቸውም ጠማማና ግራ የሚያጋቡ አይደሉም።

9. በጥልቅ ለሚያስተውሉ ሁሉም ቀና ናቸው፤ዕውቀት ላላቸውም ስሕተት የለባቸውም።

10. ከብር ይልቅ ምክሬን፣ከንጹሕ ወርቅ ይልቅ ዕውቀትን ምረጡ፤

11. ጥበብ ከቀይ ዕንቍ ይበልጥ ውድ ናትና፤ከምትመኙት ነገር ሁሉ አንዳች የሚስተካከላት የለም።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 8