ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 8:14-22 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

14. ምክርና ትክክለኛ ፍርድ የእኔ ናቸው፤ማስተዋል አለኝ፤ ብርታት አለኝ።

15. ነገሥታት በእኔ ይነግሣሉ፤ገዦችም ትክክል የሆነውን ሕግ ይደነግጋሉ፤

16. መሳፍንት በእኔ ይገዛሉ፤በምድር ላይ የሚገዙ መኳንንትም ሁሉ በእኔ ያስተዳድራሉ።

17. የሚወዱኝን እወዳቸዋለሁ፤ተግተው የሚሹኝም ያገኙኛል።

18. ሀብትና ክብር፣ዘላቂ ብልጽግናና ስኬት በእኔ ዘንድ አሉ።

19. ፍሬዬ ከንጹሕ ወርቅ ይበልጣል፤ስጦታዬም ከነጠረ ብር።

20. እኔ በጽድቅ መንገድ እሄዳለሁ፤በፍትሕም ጐዳና እጓዛለሁ፤

21. ለሚወዱኝ ብልጽግና እሰጣለሁ፤ግምጃ ቤታቸውንም እሞላለሁ።

22. እግዚአብሔር ከቀድሞ ሥራዎቹ በፊት፣የተግባሮቹ መጀመሪያ አድርጎ አመጣኝ፡

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 8