ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 6:2-9 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

2. በተናገርኸው ነገር ብትጠመድ፣ከአፍህ በወጣውም ቃል ብትያዝ፣

3. ልጄ ሆይ፤ ራስህን ለማዳን ይህን አድርግ፤በጎረቤትህ እጅ ስለ ወደቅህ፣ሄደህ ራስህን አዋርድ፤ጎረቤትህን አጥብቀህ ነዝንዘው።

4. ዐይኖችህ እንቅልፍ አይያዛቸው፣ሽፋሽፍቶችህም አያንጐላጁ።

5. ከአዳኝ እጅ እንዳመለጠች ሚዳቋ፣ከአጥማጅ ወጥመድ እንዳፈተለከች ወፍ ራስህን አድን።

6. አንተ ታካች፤ ወደ ጒንዳን ሂድ፤ዘዴውን አስተውለህ ጠቢብ ሁን፤

7. አዛዥ የለውም፤አለቃም ሆነ ገዥ የለውም፤

8. ሆኖም ግን በበጋ ምግቡን ያከማቻል፤በመከርም ወቅት ቀለቡን ይሰበስባል።

9. አንተ ታካች፤ እስከ መቼ ትተኛለህ?ከእንቅልፍህስ መቼ ትነሣለህ?

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 6