ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 31:8-15 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

8. “ስለ ራሳቸው መናገር ለማይችሉት፣ለችግረኞችም ሁሉ መብት ተሟገት።

9. ተናገር፤ በቅንነትም ፍረድ፤የምስኪኖችንና የድኾችን መብት አስከብር።”

10. ጠባየ መልካምን ሚስት ማን ያገኛታል?ከቀይ ዕንቊ እጅግ ትበልጣለች።

11. ባሏ ሙሉ በሙሉ ይተማመንባታል፤የሚጐድልበትም ነገር የለም።

12. በሕይወት ዘመኗ ሁሉ፣መልካም ታደርግለታለች እንጂ አትጐዳውም።

13. የበግ ጠጒርና የተልባ እግር መርጣ፣ሥራ በሚወዱ እጆቿ ትፈትላቸዋለች።

14. እንደ ንግድ መርከብ፣ምግቧን ከሩቅ ትሰበስባለች።

15. ገና ሳይነጋ ትነሣለች፤ለቤተ ሰቧ ምግብ፣ለሴት አገልጋዮቿም ድርሻቸውን ትሰጣለች።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 31