ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 31:19-30 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

19. በእጇ እንዝርት ትይዛለች፤በጣቶቿም ዘንጒን ታሾራለች።

20. ክንዶቿን ለድኾች ትዘረጋለች፣እጆቿንም ለችግረኞች ፈታ ታደርጋለች።

21. በረዶ ቢጥል ለቤተ ሰዎቿ አትሠጋም፤ሁሉም ቀይ ልብስ ለብሰዋልና።

22. ለመኝታዋ የዐልጋ ልብስ ትሠራለች፤ቀጭን በፍታና ሐምራዊ ልብስ ለብሳለች።

23. ባሏ በአገር ሽማግሌዎች መካከልበአደባባይ በተቀመጠ ጊዜ የተከበረ ነው።

24. የበፍታ መጐናጸፊያዎችን ሠርታ ትሸጣለች፤ለነጋዴዎችም ድግ ታቀርባለች።

25. ብርታትንና ሞገስን ተጐናጽፋለች፤መጭውን ጊዜ በደስታ ትቀበላለች።

26. በጥበብ ትናገራለች፤በአንደበቷም ቀና ምክር አለ።

27. የቤተ ሰዎቿን ጒዳይ በትጋት ትከታተላለች፤የስንፍና እንጀራ አትበላም።

28. ልጆቿ ተነሥተው፤ ቡርክት ይሏታል፤ባሏም እንዲሁ፤ ሲያመሰግናትም እንዲህ ይላል፤

29. “ብዙ ሴቶች መልካም አድርገዋል፤አንቺ ግን ሁሉንም ትበልጫለሽ።”

30. ቊንጅና አታላይ ነው፤ ውበትም ይረግፋል፤ እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት ግን የተመሰገነች ናት።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 31