ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 3:20-27 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

20. በዕውቀቱ ቀላያት ተከፈሉ፤ደመናትም ጠልን አንጠበጠቡ።

21. ልጄ ሆይ፤ ትክክለኛ ፍርድንና አስተውሎ መለየትን ጠብቅ፤እነዚህ ከእይታህ አይራቁ፤

22. ለነፍስህ ሕይወት፣ለዐንገትህም ጌጥ ይሆናሉ።

23. ከዚያም መንገድህን በሰላም ትሄዳለህ፤እግርህም አይሰናከልም፤

24. ስትተኛ አትፈራም፤ትተኛለህ እንቅልፍህም ጣፋጭ ይሆናል።

25. ድንገተኛን መከራ፣በክፉዎች ላይ የሚደርሰውንም ጥፋት አትፍራ፤

26. እግዚአብሔር መታመኛህ ይሆናልና፤እግርህንም በወጥመድ ከመያዝ ይጠብቃል።

27. ማድረግ እየቻልህለሚገባቸው መልካም ነገር ከማድረግ አትቈጠብ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 3