ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 3:1-11 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. ልጄ ሆይ፤ ትምህርቴን አትርሳ፤ትእዛዛቴን በልብህ ጠብቅ፤

2. ቀኖችን ይጨምሩልሃል፤ ዓመቶችንም ያረዝሙልሃል፤ሕይወት፣ ሀብትንና ሰላምን ያበዙልሃል።

3. ፍቅርና ታማኝነት ከቶ አይለዩህ፤በዐንገትህ ዙሪያ እሰራቸው፤በልብህም ጽላት ላይ ጻፋቸው።

4. በዚያን ጊዜ ሞገስንና መልካም ስምን፣በእግዚአብሔርና በሰው ዘንድ ታገኛለህ።

5. በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፤በራስህ ማስተዋል አትደገፍ፤

6. በመንገድህ ሁሉ እርሱን ዕወቅ፤እርሱም ጐዳናህን ቀና ያደርገዋል።

7. በራስህ አስተያየት ጠቢብ ነኝ አትበል፤ እግዚአብሔርን ፍራ፤ ከክፉም ራቅ።

8. ይህም ለሰውነትህ ጤንነትን፣ለዐጥንትህም ልምላሜን ያመጣልሃል።

9. እግዚአብሔርን በሀብትህ፣ከምርትህ ሁሉ በኵራት አክብረው፤

10. ይህን ብታደርግ፣ ጎተራህ ሞልቶ ይትረፈረፋል፤መጥመቂያህም በአዲስ የወይን ጠጅ ቲፍ ብሎ ይሞላል።

11. ልጄ ሆይ፤ የእግዚአብሔርን ተግሣጽ አትናቅ፤በዘለፋውም አትመረር፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 3