ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 26:7-26 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

7. በቂል አንደበት የሚነገር ምሳሌ፣ሰላላ የሽባ ሰው እግር ነው።

8. ለተላላ ክብር መስጠት፣በወንጭፍ ላይ ድንጋይ እንደ ማሰር ነው።

9. በአላዋቂ አንደበት የሚነገር ምሳሌ፣በሰካራም እጅ እንዳለ እሾኽ ነው።

10. ቂልን ወይም የትኛውንም ዐላፊ አግዳሚ የሚቀጥር፣ፍላጻውን በነሲብ እየወረወረ ወገኖቹን እንደሚያቈስል ቀስተኛ ነው።

11. ውሻ ወደ ትፋቱ እንደሚመለስ ሁሉ፣ተላላም ቂልነቱን ይደጋግማል።

12. ራሱን እንደ ጠቢብ የሚቈጥረውን ሰው አይተሃልን?ከእርሱ ይልቅ ለተላላ ተስፋ አለው።

13. ሰነፍ፣ “በመንገድ ላይ አንበሳ አለ፤አስፈሪ አንበሳ በአውራ ጐዳና ላይ ይጐማለላል” ይላል።

14. መዝጊያ በማጠፊያው ላይ እንደሚዞር፣ሰነፍም በዐልጋው ላይ ይገላበጣል።

15. ሰነፍ እጁን ወጭት ውስጥ ያጠልቃል፤ወደ አፉ ለመመለስ ግን እጅግ ይታክታል።

16. በማስተዋል መልስ ከሚሰጡ ከሰባት ሰዎች ይልቅ፣ሰነፍ ራሱን ጠቢብ አድርጎ ይቈጥራል።

17. በሌሎች ጠብ ጥልቅ የሚል መንገደኛ፣የውሻ ጆሮ እንደሚይዝ ሰው ነው።

18. ትንታግ ወይም የሚገድል ፍላጻ እንደሚወረውር ዕብድ፣

19. “ቀልዴን እኮ ነው” እያለባልንጀራውን የሚያታልል ሰውም እንደዚሁ ነው።

20. ዕንጨት ከሌለ እሳት ይጠፋል፤አሾክሻኪ ከሌለም ጠብ ይበርዳል።

21. ከሰል ፍምን፣ ዕንጨትም እሳትን እንደሚያቀጣጥል፣አዋኪ ሰውም ጠብን ያባብሳል።

22. የሐሜተኛ ቃል እንደ ጣፋጭ ጒርሻ ነው፤ወደ ሰው ውስጠኛው ክፍል ዘልቆ ይገባል።

23. ክፋትን በልብ ቋጥሮ ለስላሳ ቃል የሚናገር ከንፈር፣በብር ፈሳሽ እንደ ተለበጠ የሸክላ ዕቃ ነው።

24. ተንኰለኛ በከንፈሩ ይሸነግላል፤በልቡ ግን ክፋትን ይቋጥራል።

25. ንግግሩ ማራኪ ቢሆንም አትመነው፤ሰባት ርኵሰት ልቡን ሞልቶታልና።

26. ተንኰሉ በሽንገላው ይሸፈን ይሆናል፤ነገር ግን ክፋቱ በጉባኤ ይገለጣል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 26