ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 26:13-19 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

13. ሰነፍ፣ “በመንገድ ላይ አንበሳ አለ፤አስፈሪ አንበሳ በአውራ ጐዳና ላይ ይጐማለላል” ይላል።

14. መዝጊያ በማጠፊያው ላይ እንደሚዞር፣ሰነፍም በዐልጋው ላይ ይገላበጣል።

15. ሰነፍ እጁን ወጭት ውስጥ ያጠልቃል፤ወደ አፉ ለመመለስ ግን እጅግ ይታክታል።

16. በማስተዋል መልስ ከሚሰጡ ከሰባት ሰዎች ይልቅ፣ሰነፍ ራሱን ጠቢብ አድርጎ ይቈጥራል።

17. በሌሎች ጠብ ጥልቅ የሚል መንገደኛ፣የውሻ ጆሮ እንደሚይዝ ሰው ነው።

18. ትንታግ ወይም የሚገድል ፍላጻ እንደሚወረውር ዕብድ፣

19. “ቀልዴን እኮ ነው” እያለባልንጀራውን የሚያታልል ሰውም እንደዚሁ ነው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 26