ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 26:10-18 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

10. ቂልን ወይም የትኛውንም ዐላፊ አግዳሚ የሚቀጥር፣ፍላጻውን በነሲብ እየወረወረ ወገኖቹን እንደሚያቈስል ቀስተኛ ነው።

11. ውሻ ወደ ትፋቱ እንደሚመለስ ሁሉ፣ተላላም ቂልነቱን ይደጋግማል።

12. ራሱን እንደ ጠቢብ የሚቈጥረውን ሰው አይተሃልን?ከእርሱ ይልቅ ለተላላ ተስፋ አለው።

13. ሰነፍ፣ “በመንገድ ላይ አንበሳ አለ፤አስፈሪ አንበሳ በአውራ ጐዳና ላይ ይጐማለላል” ይላል።

14. መዝጊያ በማጠፊያው ላይ እንደሚዞር፣ሰነፍም በዐልጋው ላይ ይገላበጣል።

15. ሰነፍ እጁን ወጭት ውስጥ ያጠልቃል፤ወደ አፉ ለመመለስ ግን እጅግ ይታክታል።

16. በማስተዋል መልስ ከሚሰጡ ከሰባት ሰዎች ይልቅ፣ሰነፍ ራሱን ጠቢብ አድርጎ ይቈጥራል።

17. በሌሎች ጠብ ጥልቅ የሚል መንገደኛ፣የውሻ ጆሮ እንደሚይዝ ሰው ነው።

18. ትንታግ ወይም የሚገድል ፍላጻ እንደሚወረውር ዕብድ፣

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 26