ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 25:1-7 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. እነዚህ የይሁዳ ንጉሥ የሕዝቅያስ ሰዎች የቀዷቸው ሌሎች የሰሎሞን ምሳሌዎች ናቸው፦

2. ነገርን መሰወር ለእግዚአብሔር ክብሩ ነው፤ነገርን ፈልፍሎ ማውጣት ግን ለነገሥታት ክብራቸው ነው።

3. ሰማያት ከፍ ያሉ እንደሆኑ፣ ምድርም ጥልቅ እንደሆነች ሁሉ፣የነገሥታትም ልብ እንደዚሁ አይመረመርም።

4. ከብር ዝገትን አስወግድ፤አንጥረኛውም ንጹሕ ነገር ያገኛል፤

5. ክፉን ከንጉሥ ፊት አርቅ፤ዙፋኑም በጽድቅ ትጸናለች።

6. በንጉሥ ፊት ራስህን ከፍ ከፍ አታድርግ፤በታላላቆች መካከል መገኘትም አይመርህ፤

7. በትልቅ ሰው ፊት ከሚያዋርድህ፣ራሱ፣ “ወደዚህ ከፍ በል” ቢልህ ይሻላልና።በዐይንህ ያየኸውን ሁሉ፣

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 25