ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 24:9-14 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

9. የተላላ ዕቅድ ኀጢአት ነው፤ሰዎችም ፌዘኛን ይጸየፋሉ።

10. በመከራ ጊዜ ፈራ ተባ ካልህ፣ዐቅምህ ምንኛ ደካማ ነው!

11. ወደ ሞት የሚነዱትን ታደጋቸው፤እየተጐተቱ ለዕርድ የሚሄዱትን አድናቸው።

12. አንተም፣ “ስለዚህ ነገር ምንም አላውቅም” ብትል፣ልብን የሚመረምር እርሱ አያስተውልምን?ሕይወትህን የሚጠብቃት እርሱ አያውቅምን?ለእያንዳንዱስ እንደ ሥራው መጠን አይከፍለውምን?

13. ልጄ ሆይ፤ መልካም ነውና ማር ብላ፤የማር ወለላም ጣዕም ይጣፍጥሃል።

14. ጥበብም ለነፍስህ እንደዚሁ ጣፋጭ እንደሆነች ዕወቅ፤ብታገኛት ለነገ አለኝታ ይኖርሃል፤ተስፋህም ከንቱ አይሆንም።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 24