ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 23:7-21 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

7. ሁል ጊዜ ስለ ዋጋ የሚያሰላ ሰው ነውና፤“ብላ፣ ጠጣ” ይልሃል፤ልቡ ግን ከአንተ ጋር አይደለም።

8. የበላሃት ትንሿ እንኳ ታስመልስሃለች፤የምስጋና ቃልህንም ከንቱ ታደርጋለህ።

9. ከጅል ጋር አትነጋገር፤የቃልህን ጥበብ ያንኳስሳልና።

10. የጥንቱን የወሰን ምልክት አታፋልስ፤አባት የሌላቸውንም ልጆች መሬት አትግፋ፤

11. ታዳጊያቸው ብርቱ ነውና፤እርሱ ይፋረድላቸዋል።

12. ልብህን ለምክር፣ጆሮህንም ለዕውቀት ቃል ስጥ።

13. ልጅን ከመቅጣት ወደ ኋላ አትበል፤በአርጩሜ ብትገርፈው አይሞትም።

14. በአርጩሜ ቅጣው፤ነፍሱንም ከሞት አድናት።

15. ልጄ ሆይ፤ ልብህ ጠቢብ ቢሆን፣የእኔም ልብ ሐሤት ያደርጋል፤

16. ከንፈሮችህ ትክክሉን ቢናገሩ፣ውስጣዊ ሁለንተናዬ ሐሤት ያደርጋል።

17. ልብህ በኀጢአተኞች አይቅና፤ነገር ግን ዘወትር እግዚአብሔርን ለመፍራት ትጋ።

18. ለነገ ርግጠኛ አለኝታ ይኖርሃል፤ተስፋህም ከንቱ አይሆንም።

19. ልጄ ሆይ አድምጥ፤ ጠቢብም ሁን፤ልብህም ከትክክለኛው መንገድ አይውጣ።

20. ብዙ የወይን ጠጅ ከሚጠጡ፣ሥጋ ከሚሰለቅጡ ጋር አትወዳጅ፤

21. ሰካራሞችና ሆዳሞች ድኾች ይሆናሉና፤እንቅልፋምነትም ቡትቶ ያለብሳቸዋል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 23