ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 23:1-7 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. ከገዥ ጋር ለመብላት በምትቀመጥበት ጊዜ፣በፊትህ ያለውን በሚገባ አስተውል፤

2. ስግብግብም ብትሆን እንኳ፣በጒሮሮህ ላይ ካራ አጋድምበት፤

3. የእርሱ ጣፋጭ መብል አያስጐምጅህ፤ምግቡ አታላይ ነውና።

4. ሀብት ለማግኘት ስትል ራስህን አታድክም፤ሐሳብህን የመግታት ጥበብ ይኑርህ።

5. በሀብት ላይ ዐይንህን ብትጥል፤ወዲያው ይጠፋል፤ወደ ሰማይ እንደሚበርር ንስር፣ በርግጥ ክንፍ አውጥቶ ይበራል፤

6. የስስታምን ምግብ አትብላ፤ጣፋጭ መብሉም አያስጐምጅህ፤

7. ሁል ጊዜ ስለ ዋጋ የሚያሰላ ሰው ነውና፤“ብላ፣ ጠጣ” ይልሃል፤ልቡ ግን ከአንተ ጋር አይደለም።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 23