ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 22:6-20 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

6. ልጅን የሚሄድበትን መንገድ አስተምረው፤በሚሸመግልበት ጊዜ ከዚያ ፈቀቅ አይልም።

7. ባለጠጋ ድኻን ይገዛል፤ተበዳሪም የአበዳሪ ባሪያ ነው።

8. ክፋትን የሚዘራ መከራን ያጭዳል፤የቊጣውም በትር ይጠፋል።

9. ቸር ሰው ራሱ ይባረካል፤ምግቡን ከድኾች ጋር ይካፈላልና።

10. ፌዘኛን አስወጣው፤ ጠብ ይወገዳል፤ጥልና ስድብም ያከትማል።

11. የልብ ንጽሕናን ለሚወድና ንግግሩም ሞገስ ላለው ሰው፣ንጉሥ ወዳጁ ይሆናል።

12. የእግዚአብሔር ዐይኖች ዕውቀትን ይጠብቃሉ፤የማይታመኑትን ሰዎች ቃል ግን እርሱ ከንቱ ያደርጋል።

13. ሰነፍ፣ “አንበሳ ውጪ አለ፤መንገድ ላይ እገደላለሁ” ይላል።

14. የአመንዝራ ሴት አፍ ጥልቅ ጒድጓድ ነው፤ እግዚአብሔር የተቈጣውም ይገባበታል።

15. ሞኝነት በሕፃን ልብ ታስሮአል፤የተግሣጽ በትር ግን ከእርሱ ያርቅለታል።

16. ሀብቱን ለማካበት ድኻን የሚበድል፣ለባለጠጋም ስጦታ የሚያቀርብ፣ ሁለቱም ይደኸያሉ።

17. የጠቢባንን ቃል ልብ ብለህ ስማ፤ልብህም ወደ ትምህርቴ ያዘንብል፤

18. በልብህ ስትጠብቃቸው፣ሁሉም በከንፈሮችህ ላይ የተዘጋጁ ሲሆኑ ደስ ይላልና።

19. ስለዚህ እምነትህ በእግዚአብሔር ላይ እንዲሆን፣ዛሬ አንተን ራስህን አስተምርሃለሁ።

20. የምክርና የዕውቀት ቃል የሆኑ፣መልካም ትምህርቶችን አልጻፍሁልህምን?

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 22