ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 21:2-10 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

2. ለሰው መንገዱ ሁሉ ቀና ይመስለዋል፤ እግዚአብሔር ግን ልብን ይመዝናል።

3. ከመሥዋዕት ይልቅ ጽድቅንና ፍትሕን ማድረግ፣ በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነት አለው።

4. ትዕቢተኛ ዐይን፣ እብሪተኛ ልብ፣የክፉዎችም መብራት ኀጢአት ናቸው።

5. የትጒህ ሰው ዕቅድ ወደ ትርፍ ያመራል፤ችኰላም ወደ ድኽነት ያደርሳል።

6. በሐሰተኛ አንደበት የተገኘ ሀብት፣በኖ የሚጠፋ ተን፣ ለሞትም የሚያበቃ ወጥመድ ነው።

7. ክፉዎችን ዐመፃቸው ይጠራርጋቸዋል፤ቅን ነገር ማድረግ አይወዱምና።

8. የበደለኛ መንገድ ጠማማ ነው፤የንጹሕ ሰው ጠባይ ግን ቀና ነው።

9. ከጨቅጫቃ ሚስት ጋር በአንድ ቤት ከመኖር፣በጣራ ላይ ጥግ ይዞ መኖር ይሻላል።

10. ክፉ ሰው ክፋትን አጥብቆ ይመኛል፤ባልንጀራውም ከእርሱ ዘንድ ርኅራኄን አያገኝም።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 21