ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 21:17-24 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

17. ቅንጦትን የሚወድ ይደኸያል፤የወይን ጠጅና ዘይት የሚወድም ባለጠጋ አይሆንም።

18. ክፉ ሰው ለጻድቅ፣ወስላታም ለቅን ሰው ወጆ ይሆናል።

19. ከጨቅጫቃና ከቊጡ ሚስት ጋር ከመኖር፣በምድረ በዳ መኖር ይሻላል።

20. በጠቢብ ቤት ምርጥ ምግብና ዘይት ተከማችቶ ይገኛል፤ተላላ ሰው ግን ያለ የሌለውን ያሟጥጣል።

21. ጽድቅንና ፍቅርን የሚከተል፤ሕይወትን ብልጽግናንና ክብርን ያገኛል።

22. ጠቢብ የኀያላንን ከተማ ቅጥር ጥሶ ይገባል፤መታመኛ ምሽጋቸውንም ያፈርሳል።

23. አንደበቱንና ምላሱን የሚቈጣጠር፣ራሱን ከመቅሠፍት ይጠብቃል።

24. ትዕቢተኛና ኵሩ ሰው፣ ኋፌዘኛቃ ይባላል፤በጠባዩም እብሪተኛ ነው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 21