ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 20:2-8 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

2. የንጉሥ ቊጣ እንደ አንበሳ ግሣት ነው፤የሚያስቈጣውም ሰው ሕይወቱን ለመከራ ይዳርጋል።

3. ከጠብ መራቅ ለሰው ክብሩ ነው፤ተላላ ሁሉ ግን ለጥል ይቸኵላል።

4. ሰነፍ ሰው በወቅቱ አያርስም፤ስለዚህ በመከር ወራት ይፈልጋል፤አንዳችም አያገኝም።

5. የሰው ልብ ሐሳብ እንደ ጥልቅ ውሃ ነው፤አስተዋይ ሰው ግን ከዚያ ቀድቶ ያወጣዋል።

6. ብዙ ሰው ጽኑ ፍቅር እንዳለው ይናገራል፤ታማኝን ሰው ግን ማን ሊያገኘው ይችላል?

7. ጻድቅ ነቀፋ የሌለበት ሕይወት ይመራል፤ከእርሱም በኋላ የሚከተሉት ልጆቹ ቡሩካን ናቸው።

8. ንጉሥ ለፍርድ ዙፋኑ ላይ በሚቀመጥበት ጊዜ፣ክፉውን ሁሉ በዐይኖቹ አበጥሮ ይለያል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 20