ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 20:19-26 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

19. ሐሜተኛ ምስጢር ያባክናል፤ስለዚህ ለፍላፊን ሰው አርቀው።

20. አባቱን ወይም እናቱን የሚሰድብ፣መብራቱ በድቅድቅ ጨለማ ይጠፋል።

21. ከጅምሩ ወዲያው የተገኘ ርስት፣በመጨረሻ በረከት አይኖረውም።

22. “ለደረሰብኝ በደል ብድሬን ባልመልስ!” አትበል፤ እግዚአብሔርን ጠብቅ፤ እርሱ ይታደግሃል።

23. ሁለት ዐይነት ሚዛን በእግዚአብሔር ዘንድ አጸያፊ ነው፤ዐባይ ሚዛን አይወደድም።

24. የሰው አካሄዱ በእግዚአብሔር ይመራል፤ሰውስ የገዛ መንገዱን እንዴት ማስተዋል ይችላል?

25. በችኰላ ስእለት መሳል፣ከተሳሉም በኋላ ማቅማማት ለሰው ወጥመድ ነው።

26. ጠቢብ ንጉሥ ክፉዎችን አበጥሮ ይለያል፤የመውቂያ መንኰራኵርንም በላያቸው ላይ ይነዳል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 20