ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 19:1-9 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. ንግግሩ ጠማማ ከሆነ ዐጒል ሰው ይልቅ፣ያለ ነውር የሚሄድ ድኻ ሰው ይሻላል።

2. ዕውቀት አልባ የሆነ ቀናዒነት መልካም አይደለም፤ጥድፊያም መንገድን ያስታል።

3. ሰው በራሱ ተላላነት ሕይወቱን ያበላሻል፤በልቡ ግን እግዚአብሔርን ያማርራል።

4. ሀብት ብዙ ወዳጅ ታፈራለች፤ድኻን ግን ወዳጁ ገሸሽ ያደርገዋል።

5. ሐሰተኛ ምስክር ከቅጣት አያመልጥም፤ውሸት የሚነዛም ሳይቀጣ አይቀርም።

6. ብዙ ሰዎች በገዥ ዘንድ ሞገስ ለማግኘት ያሸረግዳሉ፤ስጦታን ከሚሰጥ ሰው ጋር ሁሉም ወዳጅ ነው።

7. ድኻ በሥጋ ዘመዶቹ ሁሉ የተጠላ ነው፤ታዲያ ወዳጆቹማ የቱን ያህል ይሸሹት!እየተከታተለ ቢለማመጣቸውም፣ከቶ አያገኛቸውም።

8. ጥበብን ገንዘቡ የሚያደርጋት ነፍሱን ይወዳል፤ማስተዋልን የሚወዳት ይሳካለታል።

9. ሐሰተኛ ምስክር ከቅጣት አያመልጥም፤ውሸት የሚነዛም ይጠፋል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 19