ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 17:5-12 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

5. በድኾች የሚያፌዝ ፈጣሪያቸውን ይንቃል፤በሌላው ሰው መከራ ደስ የሚለው ከቅጣት አያመልጥም።

6. የልጅ ልጆች ለአረጋውያን ዘውድ ናቸው፤ወላጆችም ለልጆቻቸው አለኝታ ናቸው።

7. መልካም አነጋገር ለተላላ አይሰምርለትም፤ለገዥማ ሐሰተኛ አንደበት የቱን ያህል የከፋ ይሆል!

8. እጅ መንሻ ለሰጭው እንደ ድግምት ዕቃ ነው፤በሄደበትም ቦታ ሁሉ ይሳካለታል።

9. በደልን የሚሸፍን ፍቅርን ያዳብራል፤ነገርን የሚደጋግም ግን የልብ ወዳጆችን ይለያያል።

10. መቶ ግርፋት ተላላን ከሚሰማው ይልቅ፣ተግሣጽ ለአስተዋይ ጠልቆ ይሰማል።

11. ክፉ ሰው ዐመፅን ብቻ ይፈልጋል፤በእርሱም ላይ ጨካኝ መልእክተኛ ይላክበታል።

12. ተላላን በቂልነቱ ከመገናኘት፣ግልገሎቿን የተነጠቀችን ድብ መጋፈጥ ይሻላል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 17