ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 17:16-24 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

16. ጥበብን ለማግኘት ፍላጎት ስለሌለው፣ተላላ እጅ የገባ ገንዘብ ጥቅሙ ምንድን ነው?

17. ወዳጅ ምንጊዜም ወዳጅ ነው፤ወንድምም ለክፉ ቀን ይወለዳል።

18. ማስተዋል የጐደለው ሰው ቃል በመግባት እጅ ይመታል፤ለወዳጁም ዋስ ይሆናል።

19. ጠብ የሚወድ ኀጢአትን ይወዳል፤በሩን ከፍ አድርጎ የሚሠራም ጥፋትን ይጋብዛል።

20. ጠማማ ልብ ያለው ሰው አይሳካለትም፤በአንደበቱ የሚቀላምድም መከራ ላይ ይወድቃል።

21. ተላላ ልጅ መውለድ ሐዘን ያስከትላል፤የተላላም አባት ደስታ የለውም።

22. ደስተኛ ልብ ጥሩ መድኀኒት ነው፤የተሰበረ መንፈስ ግን ዐጥንትን ያደርቃል።

23. ክፉ ሰው ፍትሕ ለማዛባት፣በስውር ጒቦ ይቀበላል።

24. አስተዋይ ሰው ጥበብን ከፊቱ አይለያትም፤የተላሎች ዐይኖች ግን እስከ ምድር ዳርቻ ይንከራተታሉ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 17