ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 17:13-22 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

13. በበጎ ፈንታ ክፉ የሚመልስ ሰው፣ክፉ ነገር ከቤቱ አይርቅም።

14. ጠብ መጫር ግድብን እንደ መሸንቈር ነው፤ስለዚህ ጠብ ከመጫሩ በፊት ከነገር ራቅ።

15. በደለኛውን ንጹሕ ማድረግ ሆነ፣ ንጹሑን በደለኛ ማድረግ፣ሁለቱም በእግዚአብሔር ዘንድ አጸያፊ ናቸው።

16. ጥበብን ለማግኘት ፍላጎት ስለሌለው፣ተላላ እጅ የገባ ገንዘብ ጥቅሙ ምንድን ነው?

17. ወዳጅ ምንጊዜም ወዳጅ ነው፤ወንድምም ለክፉ ቀን ይወለዳል።

18. ማስተዋል የጐደለው ሰው ቃል በመግባት እጅ ይመታል፤ለወዳጁም ዋስ ይሆናል።

19. ጠብ የሚወድ ኀጢአትን ይወዳል፤በሩን ከፍ አድርጎ የሚሠራም ጥፋትን ይጋብዛል።

20. ጠማማ ልብ ያለው ሰው አይሳካለትም፤በአንደበቱ የሚቀላምድም መከራ ላይ ይወድቃል።

21. ተላላ ልጅ መውለድ ሐዘን ያስከትላል፤የተላላም አባት ደስታ የለውም።

22. ደስተኛ ልብ ጥሩ መድኀኒት ነው፤የተሰበረ መንፈስ ግን ዐጥንትን ያደርቃል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 17