ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 15:9-21 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

9. እግዚአብሔር የክፉዎችን መንገድ ይጸየፋል፤ጽድቅን የሚከታተሉትን ግን ይወዳቸዋል።

10. ከመንገድ የሚወጣ ሰው ጥብቅ ቅጣት ይጠብቀዋል፤ዕርምትን የሚጠላ ይሞታል።

11. ሲኦልና የሙታን ዓለም በእግዚአብሔር ፊት የተገለጡ ናቸው፤የሰዎች ልብ ማየቱን ያህል የታወቀ ነው!

12. ፌዘኛ መታረምን ይጠላል፤ጠቢባንንም አያማክርም።

13. ደስተኛ ልብ ፊትን ያፈካል፤የልብ ሐዘን ግን መንፈስን ይሰብራል።

14. አስተዋይ ልብ ዕውቀትን ይሻል፤የተላላ አፍ ግን ቂልነትን ያመነዥካል።

15. የተጨቈኑ ሰዎች ዘመናቸው ሁሉ የከፋ ነው፤በደስታ የተሞላ ልብ ግን የማይቋረጥ ፈንጠዝያ አለው።

16. እግዚአብሔርን ከመፍራት ጋር ያለ ጥቂት ነገር፣ሁከት ካለበት ትልቅ ሀብት ይበልጣል።

17. ፍቅር ባለበት ጐመን መብላት፣ጥላቻ ባለበት የሰባ ፍሪዳ ከመብላት ይሻላል።

18. ግልፍተኛ ሰው ጠብ ያነሣሣል፤ታጋሽ ሰው ግን ጠብን ያበርዳል።

19. የሀኬተኛ መንገድ በእሾህ የታጠረች ናት፤የቅኖች መንገድ ግን የተጠረገ አውራ ጐዳና ነው።

20. ጠቢብ ልጅ አባቱን ደስ ያሰኛል፤ተላላ ሰው ግን እናቱን ይንቃል።

21. ማመዛዘን የጐደለው ሰው ቂልነት ያስደስተዋል፤አስተዋይ ሰው ግን ቀጥተኛውን መንገድ ይከተላል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 15