ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 15:21-32 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

21. ማመዛዘን የጐደለው ሰው ቂልነት ያስደስተዋል፤አስተዋይ ሰው ግን ቀጥተኛውን መንገድ ይከተላል።

22. ምክር ሲጓደል ዕቅድ ይፋለሳል፤በብዙ አማካሪዎች ግን ይሳካል።

23. ሰው ተገቢ መልስ በመስጠት ደስታን ያገኛል፤በወቅቱም የተሰጠ ቃል ምንኛ መልካም ነው!

24. ወደ ሲኦል ከመውረድ እንዲድን፣የሕይወት መንገድ ጠቢቡን ሰው ወደ ላይ ትመራዋለች።

25. እግዚአብሔር የትዕቢተኛውን ቤት ያፈርሰዋል፤የመበለቲቱን ዳር ድንበር ግን እንዳይደፈር ይጠብቃል።

26. እግዚአብሔር የክፉውን ሰው ሐሳብ ይጸየፋል፤የንጹሓን ሐሳብ ግን ደስ ያሰኘዋል።

27. ስስታም ሰው በቤተ ሰቡ ላይ ችግር ያመጣል፤ጒቦን የሚጠላ ግን በሕይወት ይኖራል።

28. የጻድቅ ሰው ልብ የሚሰጠውን መልስ ያመዛዝናል፤የክፉ ሰው አፍ ግን ክፋትን ያጐርፋል።

29. እግዚአብሔር ከክፉዎች ሩቅ ነው፤የጻድቃንን ጸሎት ግን ይሰማል።

30. ብሩህ ገጽታ ልብን ደስ ያሰኛል፤መልካም ዜናም ዐጥንትን ያለመልማል።

31. ሕይወት ሰጪ የሆነውን ተግሣጽ የሚሰማ፣በጠቢባን መካከል ይኖራል።

32. ተግሣጽን የሚንቅ ራሱን ይንቃል፤ዕርምትን የሚቀበል ግን ማስተዋልን ያገኛል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 15