ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 15:21-26 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

21. ማመዛዘን የጐደለው ሰው ቂልነት ያስደስተዋል፤አስተዋይ ሰው ግን ቀጥተኛውን መንገድ ይከተላል።

22. ምክር ሲጓደል ዕቅድ ይፋለሳል፤በብዙ አማካሪዎች ግን ይሳካል።

23. ሰው ተገቢ መልስ በመስጠት ደስታን ያገኛል፤በወቅቱም የተሰጠ ቃል ምንኛ መልካም ነው!

24. ወደ ሲኦል ከመውረድ እንዲድን፣የሕይወት መንገድ ጠቢቡን ሰው ወደ ላይ ትመራዋለች።

25. እግዚአብሔር የትዕቢተኛውን ቤት ያፈርሰዋል፤የመበለቲቱን ዳር ድንበር ግን እንዳይደፈር ይጠብቃል።

26. እግዚአብሔር የክፉውን ሰው ሐሳብ ይጸየፋል፤የንጹሓን ሐሳብ ግን ደስ ያሰኘዋል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 15