ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 15:16-27 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

16. እግዚአብሔርን ከመፍራት ጋር ያለ ጥቂት ነገር፣ሁከት ካለበት ትልቅ ሀብት ይበልጣል።

17. ፍቅር ባለበት ጐመን መብላት፣ጥላቻ ባለበት የሰባ ፍሪዳ ከመብላት ይሻላል።

18. ግልፍተኛ ሰው ጠብ ያነሣሣል፤ታጋሽ ሰው ግን ጠብን ያበርዳል።

19. የሀኬተኛ መንገድ በእሾህ የታጠረች ናት፤የቅኖች መንገድ ግን የተጠረገ አውራ ጐዳና ነው።

20. ጠቢብ ልጅ አባቱን ደስ ያሰኛል፤ተላላ ሰው ግን እናቱን ይንቃል።

21. ማመዛዘን የጐደለው ሰው ቂልነት ያስደስተዋል፤አስተዋይ ሰው ግን ቀጥተኛውን መንገድ ይከተላል።

22. ምክር ሲጓደል ዕቅድ ይፋለሳል፤በብዙ አማካሪዎች ግን ይሳካል።

23. ሰው ተገቢ መልስ በመስጠት ደስታን ያገኛል፤በወቅቱም የተሰጠ ቃል ምንኛ መልካም ነው!

24. ወደ ሲኦል ከመውረድ እንዲድን፣የሕይወት መንገድ ጠቢቡን ሰው ወደ ላይ ትመራዋለች።

25. እግዚአብሔር የትዕቢተኛውን ቤት ያፈርሰዋል፤የመበለቲቱን ዳር ድንበር ግን እንዳይደፈር ይጠብቃል።

26. እግዚአብሔር የክፉውን ሰው ሐሳብ ይጸየፋል፤የንጹሓን ሐሳብ ግን ደስ ያሰኘዋል።

27. ስስታም ሰው በቤተ ሰቡ ላይ ችግር ያመጣል፤ጒቦን የሚጠላ ግን በሕይወት ይኖራል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 15