ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 12:4-14 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

4. መልካም ሴት ለባሏ ዘውድ ናት፤አሳፋሪ ሚስት ግን ዐጥንቱ ውስጥ እንዳለ ንቅዘት ናት።

5. የጻድቃን ሐሳብ ቀና ነው፤የክፉዎች ምክር ግን ሸር አለበት።

6. የክፉዎች ቃል ደም ለማፍሰስ ታደባለች፤የቅኖች ንግግር ግን ይታደጋቸዋል።

7. ክፉ ሰዎች ይገለበጣሉ፤ ድራሻቸውም ይጠፋል፤የጻድቃን ቤት ግን ጸንቶ ይኖራል።

8. ሰው በጥበቡ ይመሰገናል፤ጠማማ ልብ ያላቸው ግን የተናቁ ናቸው።

9. የሚበላው ሳይኖረው ከሚኵራራ ይልቅ፣ራሱን ዝቅ አድርጎ ሠራተኛ የሚያሳድር ይሻላል።

10. ጻድቅ ሰው ለእንስሳቱ ይራራል፤ክፉዎች ራሩ ቢባል እንኳ ዞሮ ዞሮ ሥራቸው ጭካኔ ነው።

11. መሬቱን የሚያርስ የተትረፈረፈ ምግብ ያገኛል፤ከንቱ ተስፋን የሚያሳድድ ግን ማመዛዘን ይጐድለዋል።

12. ኀጥኣን የክፉዎችን ምርኮ ይመኛሉ፤የጻድቅ ሥር ግን ይንሰራፋል።

13. ክፉ ሰው በእኩይ ንግግሩ ይጠመዳል፤ጻድቅ ሰው ግን ከመከራ ያመልጣል።

14. ሰው ከከንፈሩ ፍሬ የተነሣ በበጎ ነገር ይሞላል፤እንደ እጁ ሥራም ተገቢውን ዋጋ ያገኛል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 12