ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 12:12-24 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

12. ኀጥኣን የክፉዎችን ምርኮ ይመኛሉ፤የጻድቅ ሥር ግን ይንሰራፋል።

13. ክፉ ሰው በእኩይ ንግግሩ ይጠመዳል፤ጻድቅ ሰው ግን ከመከራ ያመልጣል።

14. ሰው ከከንፈሩ ፍሬ የተነሣ በበጎ ነገር ይሞላል፤እንደ እጁ ሥራም ተገቢውን ዋጋ ያገኛል።

15. ተላላ ሰው መንገዱ ትክክል መስሎ ይታየዋል፤ጠቢብ ሰው ግን ምክር ይሰማል።

16. ተላላ ሰው ቊጣው ወዲያውኑ ይታወቅበታል፤አስተዋይ ሰው ግን ስድብን ንቆ ይተዋል።

17. ሐቀኛ ምስክር በእውነት ይመሰክራል፤ሐሰተኛ ምስክር ግን ውሸት ይናገራል።

18. ግድ የለሽ ቃል እንደ ሰይፍ ይወጋል፤የጠቢብ አንደበት ግን ፈውስን ያመጣል።

19. እውነት የሚናገሩ ከንፈሮች ለዘላለም ጸንተው ይኖራሉ፤ሐሰተኛ አንደበት ግን ለቅጽበት ያህል ብቻ ነው።

20. ክፋትን በሚያውጠነጥኑ ሰዎች ልብ አታላይነት አለ፤ሰላምን የሚያራምዱ ግን ደስታ አላቸው።

21. ጻድቃን ጒዳት አያገኛቸውም፤ክፉዎች ግን በመከራ የተሞሉ ናቸው።

22. እግዚአብሔር ሐሰተኛ ከንፈርን ይጸየፋል፤በእውነተኞች ሰዎች ግን ደስ ይለዋል።

23. አስተዋይ ሰው ዕውቀቱን ይሰውራል፤የተላሎች ልብ ግን ድንቍርናን ይነዛል።

24. ትጉ እጆች ለገዥነት ሲያበቁ፣የስንፍና ፍጻሜ ግን የባርነት ሥራ ነው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 12