ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 11:9-16 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

9. ክፉ ሰው ባልንጀራውን በአፉ ያጠፋል፤ጻድቃን ግን በዕውቀት ያመልጣሉ።

10. ጻድቃን ሲሳካላቸው ከተማ ደስ ይላታል፤ክፉዎች ሲጠፉ እልልታ ይሆናል።

11. በቅኖች በረከት ከተማ ከፍ ከፍ ትላለች፤በክፉዎች አንደበት ግን ትጠፋለች።

12. ማመዛዘን የጐደለው ሰው ባልንጀራውን ያንኳስሳል፤አስተዋይ ግን አንደበቱን ይገዛል።

13. ሐሜተኛ ምስጢር አይጠብቅም፤ታማኝ ሰው ግን ምስጢር ይጠብቃል።

14. በአመራር ጒድለት መንግሥት ይወድቃል፤የመካሮች ብዛት ግን ድልን ርግጠኛ ያደርጋል።

15. ለማይታወቅ ሰው ዋስ የሚሆን መከራ ያገኘዋል፤ዋስትና ለመስጠት እጅ የማይመታ ግን ምንም አይደርስበትም።

16. ርኅሩኅ ሴት ክብር ታገኛለች፤ጒልበተኛ ሰዎች ግን ብልጽግናን ብቻ ያገኛሉ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 11