ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 1:17-26 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

17. ወፎች ፊት እያዩ ወጥመድ መዘርጋት፣ምንኛ ከንቱ ነው!

18. እነዚህ ሰዎች የሚያደቡት በገዛ ደማቸው ላይ ነው፤የሚሸምቁትም በራሳቸው ላይ ብቻ ነው።

19. ያላግባብ ለጥቅም የሚሯሯጡ ሁሉ መጨረሻቸው እንዲህ ነው፤የሕይወታቸው መጥፊያም ይኸው ነው።

20. ጥበብ በጐዳና ላይ ጮኻ ትጣራለች፤በየአደባባዩ ድምፅዋን ከፍ ታደርጋለች፤

21. ዉካታ በበዛባቸው ጐዳናዎች ላይ ትጮኻለች፤በከተማዪቱም መግቢያ በር ላይ እንዲህ ትላለች፤

22. “እናንት ብስለት የሌላችሁ ማስተዋል የሌለበት መንገዳችሁን እስከ መቼ ትወዱታላችሁ?ፌዘኞች በፌዝ ደስ የሚሰኙት፣ሞኞችስ ዕውቀትን የሚጠሉት እስከ መቼ ነው?

23. ዘለፋዬን ብትሰሙኝ ኖሮ፣ልቤን ባፈሰስሁላችሁ፣ሐሳቤንም ባሳወቅኋችሁ ነበር።

24. ነገር ግን በተጣራሁ ጊዜ እምቢ ስላላችሁኝ፣እጄንም ስዘረጋ ማንም ግድ ስላልነበረው፣

25. ምክሬን ሁሉ ስለናቃችሁ፣ዘለፋዬንም ስላልተቀበላችሁ፣

26. እኔ ደግሞ በመከራችሁ እሥቅባችኋለሁ፤መዓት በሚወርድባችሁም ጊዜ አፌዝባችኋለሁ፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 1