ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ማሕልየ መሓልይ 8:1-9 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. ምነው አንተ የእናቴን ጡት እንደ ጠባ፣እንደ ወንድሜ በሆንህ!ከዚያም ውጭ ባገኝህ፣እስምህ ነበር፤ታዲያ ማንም ባልናቀኝ!

2. እኔም ወደ አስተማረችኝ፣ወደ እናቴም ቤት፣እጅህን ይዤ በወሰድሁህ ነበር፤የምትጠጣውን ጣፋጭ የወይን ጠጅ፣የሮማኔን ጭማቂም በሰጠሁህ።

3. ግራ እጁን ተንተርሻለሁ፤ቀኝ እጁም ዐቅፎኛል።

4. እናንት የኢየሩሳሌም ቈነጃጅት፤ራሱ እስኪፈልግ ድረስ፣ፍቅርን እንዳታስነሡት ወይም እንዳትቀሰቅሱት እማጠናችኋለሁ።

5. ውዷን ተደግፋ፣ከምድረ በዳ የምትወጣ ይህች ማን ናት?ከእንኰይ ዛፍ ሥር አስነሣሁህ፤ በዚያ እናትህ ፀነሰችህ፤በዚያም ታምጥ የነበረችው አንተንወለደችህ።

6. በልብህ እንዳለ፣በክንድህም እንደምትይዘው ማኅተም አስቀምጠኝ፤ፍቅር እንደ ሞት የበረታች፣ቅናቷም እንደ መቃብር ጨካኝ ናትና፤እንደሚንቦገቦግ እሳት፣እንደ ኀይለኛም ነበልባል ትነዳለች።

7. የውሃ ብዛት ፍቅርን ሊያጠፋ አይችልም፣ፈሳሾችም አያሰጥሟትም፤ሰው የቤቱን ሀብት ሁሉስለ ፍቅር ቢሰጥፈጽሞ ይናቃል።

8. ትንሽ እኅት አለችን፤ጡትም ገና አላወጣችም፤ስለ እርሷ በምንጠየቅበት ቀንምን ማድረግ እንችል ይሆን?

9. እርሷ ቅጥር ብትሆን፣በላይዋ የብር መጠበቂያ ማማ እንሠራባታለን፤በር ብትሆን፣በዝግባ ዕንጨት እንከልላታለን።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ማሕልየ መሓልይ 8