ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሚክያስ 7 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

የእስራኤል መከራ

1. ለእኔ ወዮልኝ!የወይን ዕርሻ በሚቃረምበት ጊዜየበጋ ፍራፍሬ እንደሚለቅም ሰው ሆኛለሁ፤የሚበላ የወይን ዘለላ የለም፤የምንጓጓለት፣ ቶሎ የሚደርሰው በለስም አልተገኘም።

2. ፈሪሃ እግዚአብሔር ያደረበት ሰው ከምድር ጠፍቶአል፤አንድም እንኳ ቅን ሰው የለም፣ሰው ሁሉ ደም ለማፍሰስ ያደባል፤እያንዳንዱም ወንድሙን በመረብ ያጠምዳል።

3. እጆቹ ክፉ ለማድረግ ሠልጥነዋል፤ገዡ እጅ መንሻ ይፈልጋል፤ፈራጁ ጒቦ ይቀበላል፤ኀይለኞች ያሻቸውን ያስፈጽማሉ፤ሁሉም አንድ ላይ ያሤራሉ።

4. ከእነርሱ ይሻላል የተባለው እንደ አሜከላ፣እጅግ ቀና የተባለውም እንደ ኵርንችት ነው፤የጠባቂዎቻችሁ ቀን ደርሶአል፤የእግዚአብሔር የፍርድ ቀን መጥቶአል፤የሚሸበሩበትም ጊዜ አሁን ደርሶአል።

5. ባልንጀራህን አትመን፤በጓደኛህም አትታመን፤በዕቅፍህ ለምትተኛዋ እንኳ፣ስለምትነግራት ቃል ተጠንቀቅ።

6. ወንድ ልጅ አባቱን ይንቃል፤ሴት ልጅ በእናቷ ላይ፤ምራት በአማቷ ላይ ትነሣለች፤የሰው ጠላቶች የገዛ ቤተ ሰዎቹ ናቸውና።

7. እኔ ግን እግዚአብሔርን ተስፋ አደርጋለሁ፤አዳኜ የሆነውን አምላክ እጠብቃለሁ፤አምላኬ ይሰማኛል።

እስራኤል ትነሣለች

8. ጠላቴ ሆይ፤ በእኔ ላይ በደረሰው ደስ አይበልሽ!ብወድቅም እንኳ እነሣለሁ፤በጨለማ ብቀመጥ እንኳ፣ እግዚአብሔር ብርሃኔ ይሆናል።

9. እርሱን ስለ በደልሁ፣እስኪቆምልኝእስኪፈርድልኝም ድረስ፣ የእግዚአብሔርን ቊጣ እቀበላለሁ፤እርሱ ወደ ብርሃን ያወጣኛል፤እኔም ጽድቁን አያለሁ።

10. ጠላቴም ታያለች፤ኀፍረትንም ትከናነባለች፤“አምላክህ እግዚአብሔር የት አለ?”ያለችኝን፣ዐይኖቼ ውድቀቷን ያያሉ፤አሁንም እንኳ፣እንደ መንገድ ጭቃ ትረገጣለች።

11. ቅጥሮቻችሁን የምትሠሩበት፣ድንበራችሁንም የምታሰፉበት ቀን ይመጣል።

12. በዚያ ቀን ሰዎች፣ከአሦር እስከ ግብፅ ከተሞች፣ከግብፅ እስከ ኤፍራጥስ፣ከባሕር ወደ ባሕር፣ከተራራ ወደ ተራራ ወደ እናንተ ይመጣሉ።

13. ከሥራቸው የተነሣ፣በነዋሪዎቿ ምክንያት ምድር ባድማ ትሆናለች።

ጸሎትና ውዳሴ

14. ብቻቸውን በዱር ውስጥ፣በለመለመ መስክ የሚኖሩትን፣የርስትህ መንጋ የሆኑትን፣ሕዝብህን በበትርህ ጠብቅ፤እንደ ቀድሞው ዘመን፣በባሳንና በገለዓድ ይሰማሩ።

15. “ከግብፅ እንደ ወጣህበት ዘመን ሁሉ፣ታምራቴን አሳያቸዋለሁ።”

16. አሕዛብ ያያሉ፣ ያፍራሉም፤ኀይላቸውን ሁሉ ያጣሉ፤አፋቸውን በእጃቸው ይይዛሉ፤ጆሮአቸውም ትደነቍራለች።

17. በደረታቸው እንደሚሳቡ ፍጥረታት፣እንደ እባብም ትቢያ ይልሳሉ፤ከዋሻቸው እየተንቀጠቀጡ ይወጣሉ፤በፍርሀትም ወደ አምላካችን ወደ እግዚአብሔር ይመለሳሉ፤እናንተንም ይፈራሉ።

18. የርስቱን ትሩፍ፣ኀጢአት ይቅር የሚል፣ የሚምርእንደ አንተ ያለ አምላክ ማነው?ለዘላለም አትቈጣም፤ነገር ግን ምሕረት በማድረግ ደስ ይልሃል።

19. ተመልሰህ ትራራልናለህ፤ኀጢአታችንን በእግርህ ትረግጣለህ፤በደላችንንም ሁሉ ወደ ጥልቁ ባሕር ትጥላለህ።

20. ከቀድሞ ዘመን ጀምሮለአባቶቻችን በመሐላ ቃል እንደ ገባህላቸው፣ለያዕቆብ ታማኝነትን፣ለአብርሃምም ምሕረትን ታደርጋለህ።