ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሚክያስ 5 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

ከቤተ ልሔም ገዥ እንደሚመጣ የተሰጠ ተስፋ

1. አንቺ የጭፍሮች ከተማ ሆይ፤ጭፍሮችሽን አሰልፊ፤ከበባ ተደርጎብናልና፤የእስራኤልን ገዥ፣ጒንጩን በበትር ይመቱታል።

2. “አንቺ ግን፣ ቤተ ልሔም ኤፍራታ ሆይ፤ከይሁዳ ነገዶች መካከል ትንሿ ብትሆኚም፣አመጣጡ ከጥንት፣ከቀድሞ ዘመን የሆነ፣የእስራኤል ገዥ፣ከአንቺ ይወጣልኛል።”

3. ስለዚህ ወላዲቱ አምጣ እስክትገላገል ድረስ፣እስራኤል ትተዋለች፤የተቀሩት ወንድሞቹም፣ተመልሰው ከእስራኤላውያን ጋር ይቀላቀላሉ።

4. በእግዚአብሔር ኀይልበአምላኩ በእግዚአብሔር ስም ታላቅነት፣ጸንቶ ይቆማል፤ መንጋውንም ይጠብቃል።በዚያን ጊዜ ኀያልነቱ እስከ ምድር ዳርቻ ስለሚደርስ፣ተደላድለው ይኖራሉ።

5. እርሱም ሰላማቸው ይሆናል።አሦራዊ ምድራችንን ሲወር፣ምሽጐቻችንንም ጥሶ ሲገባ፣ሰባት እረኞችን፣እንዲያውም ስምንት አለቆችን እናስነሣበታለን።

ትድግናና ጥፋት

6. የአሦርን ምድር በሰይፍ፣የናምሩድን ምድር በተመዘዘ ሰይፍ ይገዛሉ፤አሦራዊው ምድራችንን ሲወር፣ዳር ድንበራችንን ሲደፍር፣እርሱ ነጻ ያወጣናል።

7. የያዕቆብ ትሩፍ፣በብዙ አሕዛብ መካከል ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደሚወርድ ጠል፣በሣር ላይ እንደሚጥል ካፊያ፣ሰውን እንደማይጠብቅ፣የሰውንም ልጆች ተስፋ እንደማያደርግ ሰው ይሆናል።

8. በዱር አራዊት መካከል እንዳለ አንበሳ፣በእግሩ እየጨፈላለቀ እንደሚሄድ፣የሰበረውን ማንም ሊነጥቀው እንደማይችል፣በበግ መንጋ መካከል እንዳለ፣እንደ ደቦል አንበሳ ሁሉ፣የያዕቆብም ትሩፍ፣ በአሕዛብ ዘንድ፣ በብዙም ሕዝብ መካከል እንደዚሁ ይሆናል።

9. እጅህ በጠላቶችህ ላይ በድል አድራጊነት ከፍ ከፍ ትላለች፤ጠላቶችህም ሁሉ ይጠፋሉ።

10. “በዚያን ጊዜ” ይላል እግዚአብሔር፤“ፈረሶቻችሁን ከመካከላችሁ አጠፋለሁ፤ሠረገሎቻችሁን እደመስሳለሁ።

11. የምድራችሁን ከተሞች እደመስሳለሁ፤ምሽጎቻችሁንም ሁሉ አፈርሳለሁ።

12. ጥንቈላችሁን አጠፋለሁ፤ከእንግዲህም አታሟርቱም።

13. የተቀረጹ ምስሎቻችሁን፣የማምለኪያ ዐምዶቻችሁንም ከመካከላችሁ አጠፋለሁ፤ከእንግዲህ ለእጃችሁ ሥራአትሰግዱም።

14. የአሼራ ምስልን ዐምድ ከመካከላችሁ እነቅላለሁ፤ከተሞቻችሁንም እደመስሳለሁ።

15. ያልታዘዙኝን አሕዛብ፣በቍጣና በመዓት እበቀላቸዋለሁ።”