ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሚክያስ 3:7-12 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

7. ባለ ራእዮች ያፍራሉ፤ንግርተኞችም ይዋረዳሉ፤ሁሉም ፊታቸውን ይሸፍናሉ፤ከእግዚአብሔር መልስ የለምና።”

8. እኔ ግን፣ለያዕቆብ በደሉን፣ለእስራኤልም ኀጢአቱን እነግር ዘንድኀይልን፣ በእግዚአብሔር መንፈስ፣ፍትሕና ብርታት ተሞልቻለሁ።

9. እናንት የያዕቆብ ቤት መሪዎች፣እናንት የእስራኤል ቤት ገዦች፣ፍትሕን የምትንቁ፤ትክክለኛ የሆነውንም ነገር ሁሉ የምታጣምሙ፤ ስሙ፤

10. ጽዮንን ደም በማፍሰስ፣ኢየሩሳሌምን በክፋት የምትገነቡ፤ ስሙ።

11. መሪዎቿ በጒቦ ይፈርዳሉ፤ካህናቷ ለዋጋ ሲሉ ያስተምራሉ፤ነቢያቷም ለገንዘብ ሲሉ ይናገራሉ።ነገር ግን በእግዚአብሔር ላይ ተደግፈውም፣“እግዚአብሔር በመካከላችን አይደለምን?ምንም ዐይነት ክፉ ነገር አይደርስብንም” ይላሉ።

12. ስለዚህ በእናንተ ምክንያት፣ጽዮን እንደ እርሻ ትታረሳለች፣ኢየሩሳሌም የፍርስራሽ ክምር ትሆናለች፤የቤተ መቅደሱም ኰረብታ ዐረም የበቀለበት ጒብታ ይሆናል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሚክያስ 3