ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሚክያስ 2:5-10 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

5. ስለዚህ በእግዚአብሔር ጉባኤ ውስጥ፣መሬት በዕጣ የሚያካፍል ማንም አይኖርም።

6. ነቢያቶቻቸው፣ “ትንቢት አትናገርብን፤ስለ እነዚህ ነገሮች ትንቢት አትናገር፤ውርደት አይደርስብንም” ይላሉ።

7. የያዕቆብ ቤት ሆይ፤ እንዲህ ሊባል ይገባልን?“የእግዚአብሔር መንፈስ የማይታገሥ ነውን?እንዲህ ያሉት ነገሮችንስ ያደርጋልን?”“መንገዱ ቀና ለሆነ፣ቃሌ መልካም አያደርግምን?

8. በመጨረሻ በሕዝቤ ላይ ጠላት ሆናችሁተነሣችሁ፤የጦርነት ሐሳብ ሳይኖራቸው፣በሰላም ከሚያልፉ ሰዎች ላይ፣ማለፊያ መጐናጸፊያ ገፈፋችሁ።

9. ከሚወዱት ቤታቸው፣የሕዝቤን ሴቶች አስወጣችኋቸው፤ክብሬን ከልጆቻቸው፣ለዘላለም ወሰዳችሁ።

10. ተነሡና፤ ከዚያ ሂዱ፤ይህ ማረፊያ ቦታችሁ አይደለምና፤ምክንያቱም ረክሶአል፤ክፉኛም ተበላሽቶአል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሚክያስ 2